У нас вы можете посмотреть бесплатно ማቴቴስ - ደቀ መዝሙር | ወንጌል ምንድነው? |ክፍል 1| አስፋው በቀለ (ፓ/ር) или скачать в максимальном доступном качестве, которое было загружено на ютуб. Для скачивания выберите вариант из формы ниже:
Если кнопки скачивания не
загрузились
НАЖМИТЕ ЗДЕСЬ или обновите страницу
Если возникают проблемы со скачиванием, пожалуйста напишите в поддержку по адресу внизу
страницы.
Спасибо за использование сервиса savevideohd.ru
በመጀመርያው ዘመን ክርስትያኖች .. (ማቴቴስ ) ተብለው ነበር የሚጠሩት ። ትርጉሙም ደቀመዛሙርት ማለት ነው ። ( ሐዋ 18፡17 ) ( ሐዋ 13፡52 ) (ማቴ 12፡2 ) … ለመጀመርያ ጊዜ በመፅሀፍ ቅዱስ ክርስትያኖች … Χριστιανός ክርስትያኖስ ተብለው የተጠሩት በአንፆክያ ሀገር ነው ። በርካታ ሐይማኖታዊ ፍልስፍናዎች በበዙበት በዚህ ዘመን ትክክለኛውን ወንጌል አለማወቅ ክርስቲያኑን ማህበረሰብ ተቀበዝባዥ አድርጎታል። በሰው የተፈለሰፉ "የብልጽግና ወንጌል" "የጥርመሳ ወንጌል" የእከሌ ወንጌል" ወ.ዘ.ተረፈ ክርስቲያኑን ዓለም አጥለቅልቆታል። በሰው ፈጠራ በወንጌል ስም የሚሰበኩ ሰበካዎች በሙሉ በእግዚአብሔር ቃል ሚዛን ላይ ሲቀመጡ "ወንጌል" ሳይሆን ሐዋርያው ጳውሎስ እንደተናገረው "በዓለማዊ ትምህርት ላይ የተመሠረተ ፍልስፍና" (ቆላስያስ 2:8) እና "ልዩ ወንጌል" (ገላትያ 1:8-9) እውነተኛው ወንጌል ምንድነው? ከሚለው እንጀምር። “#በወንጌል #አላፍርምና፤ አስቀድሞ ለአይሁዳዊ ደግሞም ለግሪክ ሰው፥ ለሚያምኑ ሁሉ #የእግዚአብሔር #ኃይል #ለማዳን ነውና።” (ሮሜ 1፥16) “ወንድሞች ሆይ፥ የሰበክሁላችሁን ደግሞም የተቀበላችሁትን በእርሱም ደግሞ የቆማችሁበትን በእርሱም ደግሞ #የምትድኑበትን #ወንጌል አሳስባችኋለሁ፤” (1ኛ ቆሮንቶስ 15፥1) ወንጌል "ለሚያምኑ ሁሉ የእግዚአብሔር ሐይል ለማዳን" ነው። በአጭሩ ወንጌል "የሚያድን የእግዚአብሔር ሐይል" ነው። ይህ የእግዚአብሔር ሐይል የሆነው ወንጌል የሚያድነው ከምንድነው? ከሐጢያት መሆኑ ግልጥ ነው። (ማቴዎስ 1:21) እግዚአብሔር ደህንነትን ያዘጋጀው ሐጢያት ወደ ዓለም እንደሚገባ አስቀድሞ ስላወቀና ሐጢያትም ወደ ዓለም ስለገባ ነው። ደህንነት በቀጥታ የተገናኘው ከሐጢያት ጋር ነው። እግዚአብሔር ወንጌል ያዘጋጀውም ለዚሁ ነው። “እናንተም ደግሞ የእውነትን ቃል፥ ይኸውም #የመዳናችሁን #ወንጌል፥ ሰምታችሁ ደግሞም በክርስቶስ አምናችሁ፥ በተስፋው መንፈስ በመንፈስ ቅዱስ ታተማችሁ፤” (ኤፌሶን 1፥13) ሐዋርያው ጳውሎስ ለኤፌሶን ምዕመናን በጻፈላቸው መልዕክቱ ወንጌልን "የመዳናችሁ ወንጌል" በማለት ጠርቶታል። ሰው የመዳንን ወንጌል ካልሰማ በክርስቶስ ሊያምን አይችልም። በክርስቶስ ካላመነም በመንፈስ ቅዱስ ሊታተም አይችልም። ቅደም ተከተሉ እንደሚከተለው ነው፦ 1. የመዳናችሁን ወንጌል ሰምታችሁ 2. በክርስቶስ አምናችሁ 3. በተስፋው መንፈስ በመንፈስ ቅዱስ ታተማችሁ።